የኢትዮጵያ አየር ኃይል የቀድሞ አባላት
የኢትዮጵያ አየር ኃይል የቀድሞ አባላት በዘነበወርቅ ማገገሚያ ለተጎዱ የሰራዊቱ አባላት እርዳታ አደረጉ:: ለወገን ደራሽ ወገን ነው የሚለውን ብሂል ተከትለው የቀድሞ የአየር ሀይል አባላት የበኩላቸውን አድርገዋል፡፡ይህ እገዛ እንደአመቺነቱ ወደፊትም የሚቀጥል ይሆናል፡፡ከቀድሞው አየር ኃይልአባላት በጦርነቱ ለተጎዱ የሰራዊቱ አባላት ቱታ ፣ የውስጥ ልብሶች እና ” ለአገልግሎታችሁ እናመሰግናለን ” የሚል ፅሁፍ ያለው ሹራብ ሊበረከት ችሏል፡፡ ለሴት የሰራዊቱ አባላት የንፅህና መጠበቂያ ቁሳቁሶችን ጨምሮ የተለያዩ መድሃኒቶችን አስረክቧል ። ስጦታውን ያበረከቱት አቶ ብርሀኑ ሞላ ፤ ካፒቴን ሰለሞን መንግስቱ፤ ካፒቴን ክንዴ ዳምጤ፤ ጁቴክ ሳሙኤል ዜና፤ ጁቴክ ንጉሴ አባ ናቸው፡፡